የኢደል አደሀ ሰላት

476868967 938194858501977 6754872089946381627 n
476908363 938194898501973 6446058544049524273 n
477439434 938194851835311 1665452591661235309 n
477592679 938194798501983 3998923177975294302 n

የሴቶች አረፋ አከባበር

“የአረፋ ገባተውታን የፍቸ ቅረረውታን ኸማ ድመቆ”

የሴቶች አረፋ በመስቃን ወረዳ በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ አከባበር በዙልሂጃ በ9ኛዉ ቀን (አረፋ) ሁሉም ሁጃጆች በሙሉ አርዱል አረፋ ላይ ዉቁፍ ለማድረግ ሲሄዱ ሀጅ የማያደርጉ የመካ ወንዶችም ለመኻደም ይሄዳሉ።በዛን ጊዜ ሀረሙ በጠቅላላ ባዶ ሲሆን ቀኑን ሙሉ ሀረሙ የሴቶች ብቻ እስኪመስል ድረስ በሴቶች ይጥለቀለቅ ነበር፣ የማፍጠሪያ ምግብም አዘጋጅተዉ የመካ ሴቶች ናቸዉ ቀኑን እስከ ምሽት ድረስ ሀረሙን ሞልተዉ ካዕባዉን ከበዉ በኢባዳ ስለሚያሳልፉ የሴቶች የመካ አረፋ የሚል ስያሜ ተሠጠዉ።ያን (ባህል) በየሀገሩ እየመጣ በተለያየ አከባበር የሴቶች አረፋ በሚል ስያሜ ይከበራል።ህዚህም ወረዳችን ላይ የእናቶች ዝግጅት ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል።እናቶች ቆጮ ከመፋቅ እስከ መጋገር፣ ቅቤ በማዘጋጀት፣ሚጥሚጣ በመውቀጥና ጎመን በመቀቀል ትኩረት ሰጥተው ሲሰሩ ሴት ልጃ ገረዶች ደግሞ የመኖሪያ ቤቶችን በማስዋብ፣ የመመገቢያ ቁሶችን በማፅዳት፣ የቤተሰቡን አልባሳት ሁሉ በማጠብና ሌሎች ለበዓሉ የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎችን በሚያሟሉ ስራዎች ላይ ይጠመዳሉ፡፡የሴቶች አረፋ ከዋናው አረፋ በዓል በዋዜማው የሚከበር በዓል ሲሆን በዚህ ዕለት ሴቶች የበዓሉ ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን የሚያረጋግጡበት ቀን ነው፡፡በዚሁ እለት ሴቶች የጎመን ክትፎ እና ዝሟሙጃት በማዘጋጀት እንዲሁም የቅቤ ቡና በማፍላት ቤተ-ዘመድና ጎረቤት ጠርተው በፍቅር የሚገባበዙበት፣የሚደሰቱበትና ”የአረፋ ገባተውታን የፍቸ ቅረረውታን ኸማ ድመቆ”ብለው እየተመራረቁ የሚያሳልፍት ደማቅ በዓል ነው፡፡
503581044 1023360766652052 2789269900157611546 n
504718948 1023360923318703 1541315900407552252 n
494350235 1023361083318687 8086629037100842502 n
504427402 1023360853318710 7714573826734628412 n
499801264 1023360643318731 2709570015628483413 n
503800051 1023360813318714 3282618150739189427 n
494275784 1023360713318724 3174534396424889572 n
496558516 1023360309985431 638744301922498437 n